» Events

Events Archive

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የምሁራዊ ክርክር መድረክ

አካዳሚው በተለያዩ ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ርእሰ ጉዳዮች ላይ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግና ሳይንሳዊ አሠራሮችን ለማጎልበት የወርሐዊ ገለፃ፣ የፓናል ውይይትና ምሁራዊ የክርክር መድረኮችን ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡

በዚሁ መሠረት ”በዘረመል ምህንድስና ዘዴ የሚመረቱ የግብርና ምርቶች ጥቅሞችና ስጋቶች”፣ (The Benefits and Risks of Genetically Modified Organisms) በተሰኘ የመወያያ ርእስ ዙሪያ በዘርፉ በርካታ ጥናቶችና ምርምሮችን ያደረጉ ምሁራን አወያይ በሚያነሷቸው ጥያቄዎች መሰረት በዘረመል ምህንድስና ዘዴ ተመርተው ጥቅም ላይ የሚውሉ የግብርና ምርቶች ያስከትላሉ ተብሎ ስለሚታሰቡ ጉዳቶችና በሚያስገኟቸው ጥቅሞች ዙርያ ተመራማሪዎች አተያያቸውን በሳይንሳዊ መረጃ አስደግፈው በሁለት ጎራ ተከፍለው ሙያዊ ማብራሪያ ይሰጣሉ።

መርሐግብሩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እሸቱ ጮሌ መታሰቢያ አዳራሽ ሐሙስ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት እስከ 12፡00 ሰዓት ይካሄዳል።

Read More...
  • OFAB Ethiopia Address

    Megenagna, Ethiopian Institute of Agricultural Research

  • CONTACT NUMBER

    + 251 91 174 4540